ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
ተስፋዬ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ኃላፊ ሆኖ በመሾሙ አልተደሰተም። “ከችሎታዬ በላይ እና ከፍላጎቴ ውጪ ነው የተሾምኩት” እያለ ለኃላፊዎቹ ይናገር ነበር። እያደር ደግሞ መሥሪያ ቤቱ የጭቅጭቅና የአምባጓሮ መድረክ ሆኖ አገኘው። የኢህአዴግ የፕሮፓጋንዳ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ የነበረው በረከት ስምኦን እና የደህንነት መሥሪያ ቤቱ በፕሬስ ድርጅት ስር በሚታተሙት ጋዜጦች ላይ ለሚወጡ እንከኖች የተለያዩ ትርጉሞችን እየሰጡ ያጨናንቁት ጀመር። በውስጥ ደግሞ ኢህአዴግን የሚቃወሙ የደርግ ዘመን ጋዜጠኞች በጋዜጦቹ ላይ በረቀቀ ሁኔታ መልእክታቸውን እያወጡ ተስፋዬንና ሃላፊዎቹን ያጋጩ ነበር (ለምሳሌ በአንደኛው እሁድ በክፍሌ ሙላት ሃላፊነት ይዘጋጅ በነበረው “አድማስ” የተሰኘ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ የመዝናኛ አምድ በወጣ ግጥም በመጀመሪያ ረድፍ ላይ ያሉት ፊደሎች ከላይ ወደ ታች በአንድ ላይ ሲነበቡ “ትግራይ እስክትለማ፣ ሌላው ሀገር ይድማ” የሚል ዐረፍተ ነገር ይሰሩ ነበር። በግጥሙ መውጣት አዲስ አበባ በሙሉ ነበር የታመሰው። እኛ ገለምሶ ያለነው በኢህአዴግና በኦነግ መካከል በተፈጠረው ጣጣ ሳቢያ ጋዜጣው ባይደርሰንም ወሬው በጣም popular ሆኖ ተወርቶ እንደነበረ አስታውሳለሁ)።
ተስፋዬ ገብረአብ የፕሬስ ድርጅት ኃላፊነትን የጠላበት ሌላ ምክንያትም ነበር። ይህም አዲስ ዘመን፣ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ፣…
View original post 1,119 more words